በባሕር ዳር ከተማ የከተራ ሥነ ሥርዓት በዲፖ ጣና ዳር የባሕረ ጥምቀት እየተከናወነ ነው።

35

ባሕር ዳር: ጥር 10/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ታቦታት ከመንበራቸው በካህናት እና ዲያቆናት ወረብ እና ሽብሸባ፣ በሰንበት ትምህርት ቤት መዘምራን ዝማሬ፣ በምዕመናን እልልታ እና ሆታ ታጅበው ከባሕረ ጥምቀቱ ደርሰዋል።

በሥነ ሥርዓቱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትሪያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር እና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፁዕ አቡነ አብርሃም ተገኝተዋል።

የከተራ ሥነ ሥርዓቱ በደማቅ ሃይማኖታዊ ሥርዓት እየተከበረ ነው።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበጎንደር ከተማ ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው በልዩ ድምቀት ወደ ቅዱስ ፋሲለደስ ጥምቀተ ባሕር እየወረዱ ነው።
Next articleበደብረ ማርቆስ ታቦታት ወደ ባሕረ ጥምቀት እየወረዱ ነው።