በባሕር ዳር ከተማ በዓባይ ወንዝ ዳርቻ የሚያድሩ ታቦታት በድምቀት ወደ ባሕረ ጥምቀቱ እየወረዱ ነው።

25

ባሕር ዳር: ጥር 10/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕር ዳር በተለምዶ ዓባይ ማዶ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኙ ታቦታት ከየአድባራቱ ወጥተው ወደማደሪያቸው እያመሩ ነው።

ታቦታቱ የሚወርዱት በታላቁ የዓባይ ወንዝ ዳርቻ ነው። ነገ የሚካሄደው ሥርዓተ ጥምቀትም በዚሁ ይካሄዳል። ካህናት፣ ዲያቆናት እና መዘምራን በዝማሬ፣ የእምነቱ ተከታዮች ደግሞ በእልልታ እና በኾታ ታቦታቱን እያጀቡ በመጓዝ ላይ ናቸው።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleጌጥ እና ውበት በጥምቀት
Next articleበጎንደር ከተማ ታቦታት ከመንበራቸው ወጥተው በልዩ ድምቀት ወደ ቅዱስ ፋሲለደስ ጥምቀተ ባሕር እየወረዱ ነው።