የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞትዮስ (ዶ.ር) የኖርዌይ ፍትሕ ሚኒስትር ኤምሊ ኧንገር መኸልን በጽሕፈት ቤታቸው አነጋነሩ።

21

ባሕር ዳር: ጥር 06/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ጌድዮን ጢሞትዮስ( ዶ.ር) ኖርዌይ የኢትዮጵያ የረጅም ጊዜ አጋር ከኾኑ ሀገራት መካከል አንዷ መኾኗን ገልጸዋል ።

የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት አሁን ካለበት ደረጃ ይበልጥ ለማጠናከር ኢትዮጵያ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት መግለጻቸውን ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የማኅበራዊ ትስስር ገጽ ላይ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ በመተግበር ላይ የምትገኘው የኢኮኖሚ ሪፎርም ለውጭ ኩባንያዎች የተሻለ የተሳትፎ ዕድልን የፈጠረ በመኾኑ የኖርዌይ ባለሃብቶች መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።

የኖርዌይ ፍትሕ ሚኒስትር ኤምሊ ኧንገር መኸል ኖርዌይ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንነኙነት ለማሳደግ ቁርጠኛ መኾኗን ተናገረዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘ እና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እየሠራ መኾኑን ገለጸ።
Next article“የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅሞች ማስጠበቅ ያስቻሉ ስኬታማ የዲኘሎማሲ ሥራዎች ተከናውነዋል” የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር