“ሀገራዊ ምክክር ለወጣቶች”

23

ባሕር ዳር: ጥር 6/2017 ዓ.ም (አሚኮ)ሀገራዊ ምክክር ለወጣቶች ፋይዳው የጎላ ነው። ከእነዚህም መካከል፦
✍️ ወጣቶች በነገዋ ኢትዮጵያ ላይ ባለቤትነት ተሰምቷቸው ለፖሊሲ ግብዓት የሚኾኑ ጥያቄዎችን ብሎም ሃሳቦችን እንዲያነሱ ያስችላል፤
✍️ ወጣቶች በንግግር እና በምክክር የሃሳብ ልዩነቶችን የመፍታትን ባሕል አንዲያዳብሩ የማስቻል አቅም ይኖረዋል፤
✍️ በተለያየ ፈርጅ ውስጥ የሚመደቡ ወጣቶች በችግሮቻቸው ዙሪያ በመነጋገር ሰላማዊ በኾነ መልኩ ልዩነቶችን የመፍታትን ባሕል እንዲያዳብሩ መንገዱን ይፈጥርላቸዋል፤
✍️ የሀገራዊ ምክክር ውጤቶች እና ምክረ-ሃሳቦች ሲተገበሩ የሂደቱ ዋነኛ ተዋናይ በመኾን ከሂደቱ ተጠቃሚ የሚኾኑበትን እና ሂደቱን እንዲያግዙ ምቹ መደላድል ይፈጥርላቸዋል፤
✍️ ወጣቶች በሀገራቸው ጉዳይ ባለቤት እንደመኾናቸው ሃሳባቸው ጎልቶ እንዲሰማ ያስችላል የሚሉት ከብዙ በጥቂቱ ተጠቃሽ ናቸው፡፡

ምንጭ፦ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleከሰላም ማጽናት ጎን ለጎን ሕዝብ እና መንግሥት የጣለባቸውን ኀላፊነት በመልካም ሙያዊ ሥነ ምግባር ለመወጣት ዝግጁ መኾናቸውን የብልጽግና ፓርቲ አባላት ገለጹ።
Next articleየሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤቱ የንብረት ታክስ ረቂቅ አዋጅን አጸደቀ።