ምክር ቤቱ 14ኛ መደበኛ ጉባዔውን ነገ ያካሂዳል።

50

ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 30/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 14ኛ መደበኛ ጉባዔ ነገ ይካሄዳል።

ምክር ቤቱ ነገ በሚያካሂደው መደበኛ ጉባዔ ላይ የነዳጅ ውጤቶችን የግብይት ሥርዓት ለመደንገግ በተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ላይ የንግድ እና ቱሪዝም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚያቀርበውን ሪፖርት እና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።

በተጨማሪም የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ በሕግ እና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የሚቀርበውን ሪፖርት እና የውሳኔ ሐሳብ መርምሮ እንደሚያጸድቅ ከምክር ቤቱ የማኅበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“የጤና መድኅን ወጭው ከፍተኛ ቢኾንም የሰውን ሕይዎት መታደግ እስከቻለ ድረስ እንደ ኪሳራ አናየውም” የደባርቅ ከተማ አሥተዳደር ጤና ጥበቃ ጽሕፈት ቤት
Next articleመንግሥት በክልሉ የማኅበረሰብ አቀፍ ጤና መድኅን ተጠቃሚ ለመኾን አቅም ላነሳቸው ሰዎች 1 ቢሊዮን ብር ወጭ ማድረጉን ጤና ቢሮ ገለጸ፡፡