
“380 ሄክታር የሚሸፍነው እና በሶማሌ ክልል የሚገኘው የገበታ ለሀገር ሥራ አንዱ አካል የኾነው የሸበሌ ፕሮጀክት ለወደፊት የመስፋፋት ከፍተኛ አቅም አለው።
የትኛውንም የሀገራችን ጫፍ ስንጎበኝ ኅልቆ መሳፍርት ከሌላቸው እድሎች እና ተስፋዎች ጋር እንገናኛለን። ኢትዮጵያ እያንሰራራች ነው።
በፈተናዎች ውስጥ በተለያዩ ዘርፎች በሚታዩ አስደናቂ እድገቶች ከፍ እያለች ትገኛለች። የጋራ እድገታችን ለዘላቂ ልማት እና ብልጽግና መሠረት የኾነውን ሰላምን በመጠበቅ ላይ የተመሠረተ ነው። ለትውልድ ሁሉ የፈካ መፃዒ እድል ሰላማችንን እንጠብቅ”