ብሪክስ ዘጠኝ ሀገራትን በአጋርነት ተቀበለ።

21

ባሕር ዳር: ታኅሳስ 24/2017 ዓ.ም (አሚኮ)ብሪክስ ዘጠኝ ሀገራትን በአጋርነት መቀበሉ ታውቋል፡፡ ጥምረቱ በአጋርነት የተቀበላቸው ሀገራትም ቤላሩስ፣ ቦሊቪያ፣ ኩባ፣ ኢንዶኔዥያ፣ ካዛኪስታን፣ ማሌዥያ፣ ታይላንድ፣ ኡጋንዳ እና ኡዝቤኪስታን ናቸው፡፡

ጥቅምት ወር 2024 በሩሲያ ካዛን በተካሄደው የብሪክስ ጉባኤ ላይ 13 ሀገራት ጥምረቱን በአጋርነት እንዲቀላቀሉ ግብዣ ቀርቦላቸው እንደነበር ይታወሳል፡፡ በሩሲያ፣ ቻይና፣ ሕንድ እና ብራዚል የተመሠረተው ብሪክስ ፤ ደቡብ አፍሪካን በ2010፣ ኢትዮጵያን፣ ኢራንን፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶችን እና ግብጽን ደግሞ በ2024 በአባልነት መቀበሉ ይታወቃል፡፡

እንደ ቻይና እና ሩሲያ ያሉ የዓለም ኃያላን ሀገራትን ያቀፈው ብሪክስ ከ3 ነጥብ5 ቢሊዮን የሚበልጥ ሕዝብን እንደሚወክል ዘ ሳውዝ አፍሪካን ዶት ኮም ዘግቧል፡፡

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ኑ ተዘጋጅተን እየጠበቅናችሁ ነው” የላሊበላ ሆቴሎች ማኅበር
Next article“የልደት በዓል ለላሊበላ የቱሪዝም እንቅስቃሴ ፋይዳው ከፍ ያለ ነው” የቅዱስ ላሊበላ እና አካባቢው ቱሪስት አስጎብኝ ማኅበር