በቤት ውስጥ ተደብቆ የነበረን አደንዛዥ ዕጽ መያዙን የገንዳ ውኃ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።

23

ገንዳ ውኃ: ታኅሣሥ 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በምዕራብ ጎንደር ዞን በገንዳ ውኃ ከተማ አሥተዳደር በቤት ውስጥ ተደብቆ የነበረን ሥምንት ኩንታል አደንዛዥ እጽ በማኅበረሰቡ ጥቆማና በጸጥታ ኃይሎች መያዙን የገንዳ ውኃ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

የገንዳ ውኃ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ ጽሕፈት ቤት ተወካይ ኀላፊ ኢንስፔክተር ኃይሌ ብርሃኑ እንደተናገሩት ማኅበረሰቡ ባደረገው መልካም ትብብር እና ጥቆማ መሠረት አደንዛዥ እጹ ወደማኅበረሰቡ ሊሰራጭ በታሰበበት ሰዓት ነው የተያዘው።

ልዩ ቦታው በከተማው ቀበሌ 01 በተለምዶ አዎዬ ሠፈር ተብሎ በሚጠራው ቦታ ቤት ውስጥ ተደብቆ እንደተያዘም ለአሚኮ አስረድተዋል።

የተያዘው ሰባቱ ኩንታል አደንዛዥ እጽ እና አንድ ኩንታል የአደንዛዥ እጽ ዘር መኾኑንም ጠቁመዋል።

ኢንስፔክተሩ ማኅበረሰቡ ላደረገው ትብብር አመስግነው ቀጣይም እንዲህ ዓይነት ወንጀል ሲያጋጥም ጥቆማ እንዲሰጡ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“እጅን በመታጠብ ብቻ 20 በመቶ የሚኾኑ በሽታዎችን መከላከል ይቻላል” አቶ አብዱልከሪም መንግሥቱ
Next articleበበዓል ምክንያት ወደ ላሊበላ እና ጎንደር ከተማ የሚያደርገውን በረራ እንደሚያሳድግ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ገለጸ።