“አሚኮ 24 ሰዓትና ሰባት ቀናትን የሚተጉ ባለሙያዎች ባለቤት በመሆኑ ይህ ሚዲያው አሁን ለደረሰበት እድገት አስተዋፅኦው ከፍተኛ ነው” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

18

አዲስ አበባ: ታኅሣሥ 21/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ይህንን ያሉት አሚኮ በአዲስ አበባ ያስገነባውን ዘመናዊ ስቱዲዮ ዛሬ ሲጎበኙ ባስተላለፉት መልዕክት ነው። አሚኮ ቀደምት ከምንላቸው ተቋማት አንዱ ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተቋሙ ከአነስተኛ የሥራ ክፍሎች ወጥቶ በሚያምር እና ትልቅ ስቱዲዮ በመድረሱ ደስተኛ ነኝ ብለዋል። ሚዲያው በየደረጃው እየተለወጠ ከዚህ እንዲደርስ ላደረጉ ሁሉ ምስጋናም አቅርበዋል።

የሚዲያ ውድድሩ እያደገ በመሆኑ ከዘመኑ ጋር የሚራመድ አሠራርን መከተል እንደሚገባም አስገንዝበዋል። አሚኮ ይህንን ሲገነባ በሰው ኃይልም ብቁ ባለሙያዎችን ማፍራት እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል። የሥራ ኀላፊዎች ሚዲያን ሊጠቀሙበት እንደሚገባም አሳስበዋል። መንግሥትም ሚዲያው ውጤታማ እንዲሆን እንደሚደግፍ ተናግረዋል።

አሚኮ ቀደም ብሎም በቅርበት ስናውቀው ታታሪ ጋዜጠኞች እና ባለሙያዎች 24 ሰዓትና ሰባት ቀናትን በመሥራት የሚተጉ ባለሙያዎችና አመራሮች ያሉበት መሆኑን በተግባር ያየነው ስለሆነ ይህ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ነው ያሉት።

በአንዷለም መናን

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleአሚኮ ገዥ ትርክት በመፍጠር ለሀገር ግንባታ ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ ገለጹ።
Next articleአሚኮ የኢትዮጵያውያንን ቋንቋ በመናገር የሀገር አቅምነቱን እያስመሰከረ እንደሚገኝ ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ገለጹ።