በጎንደር ከተማ የከተራ እና ጥምቀት በዓልን በሰላም ለማክበር ዝግጅት እየተደረገ ነው።

32

ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 18/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ከጎንደር ቀጠና የፀጥታ መዋቅር ጋር ወቅታዊ የሕግ ማስከበር ሥራዎችን ገምግሟል። የቀጣይ መሰረታዊ የሕግ ማስከበር ሥራዎች ላይም ውይይት ተደርጎ አቅጣጫ ተቀምጧል።

ከተራ እና የጥምቀት የሕዝብ ሰላም እና የበዓላቱ ሥርዓት ተጠብቆ እንዲከበሩ በሚቻልበት ኹኔታ ላይም ምክክር ተደርጓል። በዓላቱን ተከትሎ ሕዝብን ሰላም ለመንሳት መንሳት የሚንቀሳቀሱ አካላት እንዳይኖሩ ከወዲኹ እየተሠራ ስለመኾኑም በውይይቱ ተነስቷል።

ከመላ ሕዝቡ ጋር በመኾን አስፈላጊ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እየተከናወኑ ሥለመኾኑም ተነግሯል። ከወጣቶች ጋር በመኾን ለበዓላቱ ራሱን የቻለ እቅድ ተዘጋጅቶ በሥርዓት እንዲመራም አቅጣጫ ተቀምጧል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleተስፋችንን አታጨልሙብን
Next article“የተፈናቀሉ ዜጎችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ እና በዘላቂነት ለማቋቋም መንግሥት በትኩረት እየሠራ ነው” መንገሻ ፈንታው (ዶ.ር)