አቶ አደም ፋራህ ባሕር ዳር ገቡ።

61

ባሕር ዳር: ታኅሳስ 11/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኀላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ ባሕር ዳር ገብተዋል።

ባሕር ዳር ደጅ አዝማች በላይ ዘለቀ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)፣ የአማራ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ይርጋ ሲሳይን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኀላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

አቶ አደም ፋራህ በባሕር ዳር በሚኖራቸው ቆይታ ከአማራ ክልል ከፍተኛ መሪዎች ጋር በሰላም፣ በልማት እና በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ ይወያያሉ ተብሏል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleጸጋዎችን በመለየት እና ዘመናዊ አሠራርን በመከተል ልማትን ማፍጠን እንደሚገባ ተጠቆመ።
Next articleድጋፍ የሚሹ ወገኖች ቁጥር 80 በመቶ መቀነሱን የሰሜን ወሎ ዞን አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።