በአዊ ብሔረሰብ አሥተዳደር ባንጃ ወረዳ መንግሥት እየወሰደ ያለውን ሕግ የማስከበር እርምጃ የሚደግፍ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ተካሂዷል።

18

እንጅባራ: ታኅሣሥ 09/2017 ዓም (አሚኮ) በሰልፉ የሃይማኖት አባቶች፣ ፈረሰኞች፣ ተማሪዎች እና ልዩ ልዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተሳትፈዋል።

የባንጃ ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት እንደዘገበው መንግሥት በተደጋጋሚ የሚያቀርበውን የሰላም ጥሪ እንደግፋለን!!

ለክልላችን የሚያስፈልገው ጦርነት ሳይኾን ሰላም እና ልማት ነው!!

መንግስት ለሰላም መስፍን የሚወስዳቸውን ርምጃዎች እንደግፋለን!!

ሠላም የጋራ ሃብት ነው! በጋራ ይጠበቃል!!

ሰላም ከሌለ መማር የለም!

እኛ ተማሪዎች እስክርቢቶ እና ደብተር እንጂ የጥይት ድምፅ መስማት አንፈልግም!! የሚሉ መልዕክቶችም በሰልፉ ተላልፈዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ሰላምን በትጋት ማጽናት የሰው ልጆች ሚና ነው” አቶ አሸተ ደምለው
Next articleማኅበረሰቡ በሰላም ወጥቶ እንዲገባና ሰላም እንዲሰፍን ሁሉም ኀላፊነቱን ሊወጣ ይገባል።