“መንግሥት ሁልጊዜም ቢኾን ለሰላም በሩ ክፍት ነው፤ ትጥቅ ያነሱ ቡድኖች አሁንም ቢኾን ወደ ሰላማዊ መድረኩ እንዲመጡ ጥሪ እናቀርባለን” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ

24

ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ በአማራ ክልል እየተካሄዱ የሚገኙ ሕዝባዊ የሰላም ሰልፎችን አስመልክተው በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ የሚከተለውን መልእክት አስተላልፈዋል።

ዛሬ በተለያዩ የአማራ ክልል ከተሞች፣ የገጠር ወረዳዎች እና ቀበሌዎች ሕዝባችን ”ሰላም ለሁሉም፣ ሁሉም ለሰላም” በሚል መሪ ሃሳብ በነቂስ ወጥቶ ላሳየው የሰላም የድጋፍ ሰልፍ ምስጋና ይገባዋል።

ሰላም ወዳዱ ሕዝባችን መንግሥት ለሰላም እያቀረበ ያለውን ተደጋጋሚ ጥሪ በመደገፍ እና ጽንፈኝነትን በማውገዝ የታጠቁ ቡድኖች ወደ ሰላም እንዲመጡ ጥሪ አቅርቧል። በመኾኑም የአማራ ክልልን የሰላም እና የልማት ማዕከል ለማድረግ ሁሉም ለሰላም ዘብ ሊቆም ይገባል።

መንግሥት ሁልጊዜም ቢኾን ለሰላም በሩ ክፍት በመኾኑ ትጥቅ ያነሱ ቡድኖች ጽንፈኝነት እና ግጭት ማንንም እንደማይጠቅም በመገንዘብ ወደ ሰላማዊ መድረኩ እንዲመጡ ጥሪ እናቀርባለን።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበአየሁ ጓጉሳ ወረዳ መንግሥት እየወሰደ ያለውን ሕግ የማስከበር እርምጃ የሚደግፍ ሕዝባዊ ሰልፍ ተካሂዷል።
Next articleበአማራ ክልል በተለያዩ ከተሞች የተካሄደው ሕዝባዊ ሰልፍ ተጠናቀቀ።