ልጆቻቸው ያለችግር እንዲማሩ መንግሥት ሕግ ማስከበሩን አጠናክሮ እንዲቀጥል የዱር ቤቴ ከተማ ነዋሪዎች ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ ገለጹ።

16

ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በሰሜን ጎጃም ዞን በዱር ቤቴ ከተማ አሥተዳደር “ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም” በሚል መሪ መልዕክት ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

ሰልፈኞቹ መንግሥት በተደጋጋሚ የሚያደርገውን የሰላም ጥሪ እንደሚደግፉ እና ለዚህም እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል።

የሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፈኞች የጽንፈኛው ኀይል በንፁሀን ላይ የሚፈጽመውን ግድያ፣ ማንገላታት እና ማፈናቀል ሊያቆም ይገባል ነው ያሉት።

ሰላም የጋራ ሃብት እንደኾነም አስገንዝበዋል።

ሕጻናትን ከትምህርት ገበታቸው ማስቀረት የጽንፈኝነት ጥግ ነው ያሉት ሰልፈኞቹ ልጆቻቸው ያለችግር እንዲማሩ እንደሚፈልጉም ነው የተናገሩት።

የአማራ ሕዝብ ጥያቄዎች በውይይት እንጅ በጦርነት የሚፈቱ አይደሉም ብለዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበደቡብ ጎንደር ዞን እብናት ከተማ አሥተዳደርና እብናት ወረዳ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
Next articleበምዕራብ ጎንደር ዞን ምዕራብ አርማጭሆ ወረዳ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሠልፍ እየተካሄደ ነው።