ለክልሉ የሚያስፈልገው ጦርነት ሳይኾን ሰላም እንደኾነ የደብረ ብርሃን ከተማ ነዋሪዎች ባካሄዱት ሰላማዊ ሰልፍ ገለጹ።

26

ደብረ ብርሃን: ታኅሣሥ 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በደብረ ብርሃን ከተማ አሥተዳደር “ለሰላም ዘብ እንቁም”በሚል መሪ መልዕክት ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

በሰልፉ ላይ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ነው።

ሰልፈኞቹ በመፈክሮቻቸው ባስተላለፉት መልዕክት መንግሥት ለሰላም መስፈን የሚወስደውን ርምጃ እንደሚደግፉ ተናግረዋል።

ሰላም የጋራ ሃብት ነው ያሉት ሰልፈኞቹ በጋራ እንደሚያለሙት እና በጋራ እንደሚጠብቁትም አስረድተዋል።

መንግሥት ለሰላም መስፈን የሚወስዳቸውን ርምጃዎች እንደሚደግፉም ነው ያብራሩት።

ሰልፈኞቹ ለክልሉ የሚያስፈልገው ጦርነት ሳይኾን ሰላም እንደኾነ ነው የተናገሩት።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበነፋስ መውጫ ከተማ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
Next articleየጎንደር ነዋሪዎች ለሰላም ልዩ ትኩረት እንዲሰጡ የከተማዋ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጠየቁ።