ጽንፈኛ ቡድኑ የሚያደርሰውን ግፍ እና በደል እንደሚቃወሙ የሞጣ ከተማ ነዋሪዎች በሰላማዊ ሰልፍ ገለጹ።

26

ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በምሥራቅ ጎጃም ዞን በሞጣ ከተማ በክልሉ ሕግን ለማስከበር የሚሠራውን ሥራ የሚደግፍ እና ጽንፈኛው ቡድን የሚያደርሰውን ግፍ እና በደል የሚቃወም ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው፡፡

ሰላማዊ ሰልፈኞቹ መንግሥት በተደጋጋሚ የሚያደርገውን የሰላም ጥሪ እንደሚደግፉ ተናግረዋል።

ክልሉን የሰላም እና የልማት ማዕከል ለማድረግ ለሰላም ዘብ እንደሚቆሙ የተናገሩት ነዋሪዎቹ መንግሥት ሕግ በማስከበር የንፁሃን ሰዎችን ሕይዎት እንዲታደግ ነው የጠየቁት።

መንግሥት ለሰላም መስፈን የሚወስዳቸውን ርምጃዎች እንደሚደግፉም ባሰሙት መፈክር አረጋግጠዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበባቲ ከተማ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
Next articleበኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር መንግሥት በተደጋጋሚ ያቀረበውን የሰላም ጥሪ የሚደግፍ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።