በባቲ ከተማ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

31

ባሕር ዳር: ታኅሳስ 9/2017 ዓ.ም (አሚኮ) “ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም” በሚል መሪ መልዕክት በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር በባቲ ከተማ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

በሰልፉ ላይ ወጣቶች፣ የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች፣ ተማሪዎች እንዲሁም ነዋሪዎች ተሳታፊ ኾነዋል።

የድጋፍ ሰልፉ ተሳታፊዎች የሰላምን ዋጋ ለማወቅ የግድ ሰላም ማጣት የለብንም፤ ሰላም በገንዘብ የማይተመን ውዱ እና አስፈላጊው የሕይዎት ገጽታ ነው በማለት የተለያዩ መልዕክቶችን እያሰሙ ወደ ኳስ ሜዳ አደባባይ እየሄዱ ይገኛሉ።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሠላም” በሚል መሪ መልእከት በሰሜን ወሎ ዞን በሀራ ከተማ አሥተዳደር ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
Next articleጽንፈኛ ቡድኑ የሚያደርሰውን ግፍ እና በደል እንደሚቃወሙ የሞጣ ከተማ ነዋሪዎች በሰላማዊ ሰልፍ ገለጹ።