በሀርቡ ከተማ አሥተዳደር ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

34

ሀርቡ: ታኅሣሥ 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በደቡብ ወሎ ዞን በሀርቡ ከተማ አሥተዳደር ጽንፈኞችን የሚያወግዝ የሕግ ማስከበሩን የሚደገፍ ሕዝባዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነዉ።

በሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ ላይ በሰልፈኞች የተለያዩ መልዕክቶች እየተላለፈ ሲሆን መልዕክቶቹም፦

👉 መንግሥት በተደጋጋሚ የሚያደርገውን የሰላም ጥሪ እንደግፋለን!

👉 በደምበጫ በገርጨጭ፣ በላሊበላና በሌሎች አካባቢዎች ንፁሃንን የጨፈጨፉ ፅንፈኛ ኀይሎች ለሕግ ይቅረቡልን!

👉 ክልላችንን የሰላምና የልማት ማዕከል ለማድረግ ሁላችንም ለሰላም ዘብ እንቆማለን!

👉 መንግሥት ሕግ በማስከበር የንፁሃን ሰዎችን ገዳዮች ለሕግ ያቅርብልን!

👉 መንግሥት ለሰላም መስፈን የሚወስዳቸውን እርምጃዎች እንደግፋለን!

👉 በደጋ ዳሞት ፈረስ ቤት ከተማ ፅንፈኛው ኀይል በንፁኀን ላይ የፈፀመውን ዘግናኝ ጭፍጨፋና ግድያ በፅኑ እናወግዛለን!

👉 ንፁኀንን በግፍ እየገደሉ በአስከሬናቸው መነገድ አረመኔያዊነት ነው!

👉 የልማት ማዕከል የነበረውን ክልላችንን የጦርነት ቀጠና ለማድረግ የሚሠራው ሥራ የባንዳነትና የፅንፈኝነት ጥግ ነው!

👉 ንፁኀንን በግፍ መጨፍጨፍ የአረመኔነት ጥግ ስለሆነ ሊወገዝ ይገባዋል!

👉 ለክልላችን የሚያስፈልገው ጦርነት ሳይሆን ሰላም እና ልማት ነው!

👉 ፅንፈኛ እና ተላላኪዎች ከባዕዳን ተልዕኮ ወጥተው የሰላምን አማራጭ ሊከተሉ ይገባል!

👉 ሰላም የጋራ ሀብት ነው፤ በጋራ ይለማል በጋራ ይጠበቃል!

👉 መንግሥት ሕግ በማስከበር የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ሊያስጠብቅ ይገባል!

👉 ፅንፈኛው ኀይል በንፁሃን ላይ የሚፈፅመው ግድያ፣ ማገትና ማፈናቀል ሊቆም ይገባል!

👉 መከላከያ ሠራዊታችን፣ የፌዴራል የፀጥታ ኀይሎች እና የክልላችን የፀጥታ ኀይሎ ለከፈሉት ዋጋ ክብር እንሰጣለን!

በአንተነህ ጸጋየ

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ደብተር እና ብዕር እንጅ ጥይት አንፈልግም” የባሕር ዳር ተማሪዎች መልእክት
Next articleመንግሥት የሚወስዳቸውን የሕግ ማስከበር ሥራዎች እንደሚደግፉ የደባርቅ ከተማ ነዋሪዎች በሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ገለጹ።