“ለሰላም ዘብ እንቆማለን” በሚል መሪ መልእክት በጎንደር ከተማ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

57

ጎንደር: ታኅሣሥ 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በሰልፉ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ሲኾን ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ የሚጠይቁ መፈክሮች እየተሰሙ ነው።

👉 ክልላችን የሰላምና የልማት ማዕከል ለማድረግ ለሰላም ዘብ እንቆማለን!

👉 መንግሥት የዜጎችን ሰላም እና ደኅንነት ያስጠብቅ!

👉 መንግሥት ሰላምን ለማስከበር የሚወስዳቸውን ርምጃዎች እንደግፋለን!

👉 ህፃናት የጽንፈኛ ኀይሎች መነገጃ አይደሉም!

👉 መንግሥት በተደጋጋሚ የሚያደርገውን የሰላም ጥሪ እንደግፋለን!

👉 እኛ ተማሪዎች በሰላም መማር እንፈልጋለን!

👉 ለከተማችን የሚያስፈልገው ጦርነት ሳይኾን ንፁህ መጠጥ ውኃ ነው!

👉 ሰላም የጋራ ሃብት ነው በጋራ ይጠበቃል።

👉 እንዲሁም የፌዴራል መንግሥት ለጎንደር ከተማ እያደረገ ላለው ሁለንተናዊ ድጋፍ የሚያመሰግኑ መፈክሮች እየተሰሙ ነው።

የሰልፍ ሥነ ሥርዓቱ በፋሲለደስ ስታዲየም መዳረሻውን አድርጎ የተለያዩ መርሐ ግብሮች እየተከወኑ ነው።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበክልሉ የተፈጠረው የጸጥታ ችግር እንዲቆም እና ሰላም እንዲሰፍን የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች በሰላማዊ ሰልፍ ጠየቁ።
Next article“ደብተር እና ብዕር እንጅ ጥይት አንፈልግም” የባሕር ዳር ተማሪዎች መልእክት