በደሴ ከተማ “ጦርነት ይብቃ፣ ሰላም ይስፈን” በሚል መሪ መልዕክት ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።

80

ደሴ: ታኅሳስ 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በደሴ ከተማ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች እና የገጠር ቀበሌዎች የተውጣጡ የማኅበረሰብ ክፍሎች ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ እያካሄዱ ነው።

የተለያዩ መልእክቶችን የያዙት ሰላማዊ ሰልፈኞች “ጦርነት ይብቃ ሰላም ይስፈን” በማለት ወደ ሆጤ ስታዲዬም እየተጓዙ ነው።

በሰላማዊ ሰልፉ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የንግዱ ማኅበረሰብ፣ የመንግሥት ሰራተኞች እና የከተማው ሕዝብ እየተሳተፈ ነው።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበደብረ ማርቆስ ከተማ ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም በሚል መሪ መልዕክት ሕዝባዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
Next articleበእንጅባራ ከተማ መንግሥት እየወሰደ ያለው ሕግ የማስከበር ርምጃ የሚደግፍ ሕዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።