ዳሽን ቢራ ፋብሪካ አክሲዮን ማኅበር በደብረ ብርሃን ከተማ ለሚገኙ ተፈናቃዮች የዕለት ደራሽ ድጋፍ አደረገ።

44

ደብረ ብርሃን: ታኅሣሥ 08/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በሰላም እጦት ምክንያት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ለከፋ ችግር እንዳይጋለጡ የበኩሉን እየተወጣ መኾኑን ፋብሪካው አስታውቋል።

475 ኩንታል የበቆሎ ዱቄት ድጋፍ መደረጉን በፋብሪካው የማኅበራዊ አገልግሎት ጉዳይ ኀላፊ ጌታነህ ዝቄ ተናግረዋል።

በተፈናቃዮች ጊዜያዊ መጠለያ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ ወገኖችም የሰላም ሁኔታው ቢስተካከል ወደ ቀደመ ቀያቸው የመመለስ ፍላጎት እንዳላቸው አስረድተዋል። ለተደረገላቸው ድጋፍም አመስግነዋል።

መንግሥት ዘላቂ መፍትሄ በማመቻቸት ከችግር እንዲያላቅቃቸውም ጠይቀዋል።

ዘጋቢ:- አበበች የኋላሸት

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበፍኖተ ሰላም ከተማ ከወጣቶች ጋር በሰላም እና በልማት ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሄደ።
Next articleየውጭ ባንኮች በሀገር ውስጥ ገብተው እንዲሠሩ የሚያስችል አዋጅ ጸደቀ።