ሕዝቡ የሰጣቸውን አደራ ለመወጣት እየሠሩ እንደሚገኙ በኦሮሚያ ክልል በአጀንዳ ማሠባሠብ ሥራ ላይ እየተሳተፉ ያሉ የኅብረተሰብ ተዎካዮች ገለጹ።

33

አዲስ አበባ: ታኅሣሥ 08/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በኦሮሚያ ክልል ለሀገራዊ ምክክር የአጀንዳ ማሠባሠብ ሥራ እየተካሄደ ነው። በአጀንዳ የማሠባሠብ ሥራ መድረክ ላይ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ተወካዮች እየተሳተፉ ነው የሚገኙት።

ዛሬ እየተካሄደ ባለው የአጀንዳ ማሠባሠብ ሥራ ላይ ከ356 ወረዳዎች የተውጣጡ ከ7ሺህ በላይ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች ተወካዮች እየተሳተፉ ነው። የመድረኩ ተሳታፊዎች የመወያያ አጀንዳዎችን በመለየት ላይ እንደሚገኙም ለአሚኮ ተናግረዋል።

የኅብረተሰቡን ጥያቄዎች በማሠባሠብ በሀገር አቀፍ የምክክር መድረክ ላይ በማቅረብ ሕዝቡ የሰጣቸውን አደራ ለመወጣት እየሠሩ እንደሚገኙም የኅብረተሰቡ ተወካዮች አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበአማራ ክልል የሥነ ምግባር ግንባታ እና ሙስናን የመከላከል ጥምረት ተመሠረተ።
Next articleበፍኖተ ሰላም ከተማ ከወጣቶች ጋር በሰላም እና በልማት ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሄደ።