
ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 07/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ሰሜ (ዶ.ር) በአማራ ክልል ኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር በአርጡማ ፉርሲ ወረዳ በብሼ ኤዴዳ ቀበሌ በመገኘት የበጋ ስንዴ ዘር አስጀምረዋል።
ሚኒስትሩ ከአማራ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች ጋር በመኾን ነው ሥራውን ያስጀመሩት።
በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ የኦሮሞ ብሔረሰብ አሥተዳደር ዋና አሥተዳዳሪ አሕመድ አሊ፣ በብሔረሰብ አሥተዳደሩ የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ አሕመድ ሁሴን እና ሌሎች የክልልና የዞን አመራሮችም ተገኝተዋል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!