
አዲስ አበባ: ታኅሣሥ 07/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ኮሚሽኑ ይህን ያለው የሀገራዊ የምክክር አጀንዳዎች የማሰባሰብ ሥራ በአዳማ ከተማ በተጀመረበት መድረክ ላይ ነው።
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነሩ ፕሮፌሰር መሥፍን አርኣያ በአማራ ክልል እየተካሄደ ባለው ግጭት ምክንያት የዘገየውን የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የተሳታፊዎች ልየታ በቀጣይ አንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንደሚደረግ ጠቁመዋል።
ኮሚሽኑ በእስካሁን ቆይታው በ9 ክልሎች እና ሁለት ከተማ አሥተዳደሮች የአጀንዳ ልየታ ሥራ ማከናወኑን ተናግረዋል። በ971 የኢትዮጵያ ወረዳዎች የተሳታፊዎች ልየታ መከናወኑንም ዋና ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል።
ዘጋቢ:- ሽመልስ ዳኜ
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!