ለ25ኛው የአፍሪካ ኢቫሉዌሽን አሶሴሽን የዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መኾኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።

32

አዲስ አበባ:- ታኅሣሥ 07/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በመጪዉ ሰኔ ኢትዮጵያ ለምታዘጋጀው 25ኛው የአፍሪካ ኢቫሉዌሽን አሶሴሽን መርሐ ግብር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እየተከናወኑ መኾኑን የፕላንና ልማት ሚኒስቴር አስታውቋል። የፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ ኢቫሉዌሽን አሶሴሽን እና ከአፍሪካ ኢቫሉዌሽን አሶሴሽን ጋር በመርሐ ግብሩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ዙሪያ ውይይት አድርጓል።

በውይይቱም ኢትዮጵያ ሰኔ ላይ ለምታዘጋጀው ለዚህ አህጉራዊ ፕሮግራም ከአጋር አካላት ጋር የተለያዩ ቅድመ ዝግጅቶችን እያደረገች እንደምትገኝ የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ በረከት ፍስሃፅዮን ተናግረዋል። ይህን መድረክ ኢትዮጵያ ማዘጋጀቷ ትልቅ አቅም ይፈጥርላታል ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ኢቫሉዌሽን አሶሴሽን ፕሬዚዳንት ደረጀ ማሞ ናቸው።

የአፍሪካ ኢቫሉዌሽን አሶሴሽን ፕሬዝዳንት ሚሼ ኦውድራጎ (ዶ.ር) ፕሮግራሙ የተሳካ እንዲኾን የኢትዮጵያ መንግሥት እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

ዘጋቢ:- ቤቴል መኮንን

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በባሕር ዳር ከተማ ልዩ መለያ (ባር ኮድ) ያላደረጉ ባጃጆች አገልግሎት አይሰጡም” ከተማ አሥተዳደሩ
Next articleበቀጣይ አንድ ወር ጊዜ ውስጥ በአማራ ክልል የተሳታፊ እና የአጀንዳ ልየታ እንደሚያደርግ የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን አስታወቀ።