“ሥምምነቱ ሀገራችን በሰላማዊ መንገድ የባሕር በር ለማግኘት ለምታደርገው ጥረት የጎላ ሚና ይጫዎታል” ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ

29

ባሕር ዳር: ታኅሣሥ 03/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በቱርክ ፕሬዚዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን አደራዳሪነት በአንካራ የተካሄደው የኢትዮጵያና የሶማሊያ ድርድር የጋራ አሸናፊነት የታየበት መሆኑ ሀገራችን ለጋራ ሰላምና ልማት ከሶማሊያ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኗን ያስመሰከረ ነው ብለዋል በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልእክት፡፡

ሥምምነቱ ሀገራችን የባህር በር በሰላማዊ መንገድ ለማግኘት የምታደርገው ጥረት ለቀጠናው ምጣኔ ሃብታዊና ማኅበራዊ ትስስር የጎላ ሚና እንደሚጫወት ያመላከተ ድርድርና ውይይት ነው፤ ይህ ሥምምነት ቀጠናዊ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ፣ የዕርስ በርስ ትብብርን፣ ምጣኔ ሃብታዊ ልማትንና ብልፅግናን የሚያረጋግጥልንም ይሆናል ነው ያሉት።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም” በሚል መልእክት በላሊበላ ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።
Next articleየአማራ ክልል ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዓለም አቀፍ የጤና ምርምር ጉባዔ እያካሄደ ነው።