የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ ባሕር ዳር ገቡ።

20

ባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 03/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ሚኒስትሯ ባሕር ዳር ደጅአዝማች በላይ ዘለቀ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርሱ ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር)፣ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የማኅበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ እና የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ.ር)፣ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ኃላፊ አብዱልከሪም መንግሥቱ እና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ዶክተር መቅደስ ዳባ በባሕር ዳር በሚኖራቸው ቆይታ የአማራ ክልል ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ባዘጋጀው ዓለም አቀፍ የጤና ምርምር ጉባኤ ላይ ይሳተፋሉ ተብሏል።

ከጉባኤው ባለፈ በባሕር ዳር ከተማ የሚገኙ የጤና ተቋማትን እንደሚጎበኙ እና ከክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በጤና ዘርፍ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleኢትዮጵያ በሶማሊያ ዘላቂ እና ደኅንነቱ የተጠበቀ የወደብ አማራጭ በምታገኝበት አማራጭ ላይ የቴክኒክ ውይይቶችን ለመጀመር መስማማት ላይ ተደረሰ።
Next article“ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም” በሚል መልእክት በላሊበላ ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ እየተካሄደ ነው።