የሰላም አሰከባሪና የሚሊሻ አባላት ሰላምን በዘላቂነት ለማስፈን በቁርጠኝነት ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋገጡ።

54

ባሕር ዳር፡ ታኅሣሥ 02/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የምስራቅ ጎጃም ዞን በተለያዩ ወረዳዎችና ከተማ አሥተዳደሮች የሰላም አሰከባሪና የሚሊሻ አባላትን አሠልጥኖ እያስመረቀ ነዉ።

በምስራቅ ጎጃም ዞን በአዋበል ወረዳ ለተከታታይ ቀናት የአቅም ግንባታ ሥልጠና ሲወስዱ የነበሩ አዲስና ነባር የሰላም አሰከባሪና የሚሊሻ አባላት ሥልጠናቸውን አጠናቅቀው ተመርቀዋል።

የዞኑ መንግሥት ኮሙኒኬሽን መምሪያ መረጃ እንደሚያመለክተው ሰላም ለማስጠበቅ ሥልጠና ሲወስዱ የቆዩት የሰላም አስከባሪና የሚሊሻ አባላት ሰላምን በዘላቂነት ለማስፈን በቁርጠኝነት ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleወጣቶች ዛሬን የሚገነቡ እና ነገን የሚረከቡ በመሆናቸው በመልካም ሰብዕና መገንባት ይገባል።
Next articleበደብረ ብረሃን ከተማ አሥተዳደር አንደኛ ደረጃ የገበያ ማዕከል ሊገነባ ነው።