የአምራች ወገኖችን ሕይወት የሚቀጥፈዉን ኤች አይ ቪ ኤድስ ቫይረስ ለመከላከል በትኩረት መሥራት እንደሚገባ ተገለጸ።

30

ደብረ ብርሃን: ኅዳር 26/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የደብረ ብርሃን ኢንዱስትሪ ፓርክ የዓለም ኤች አይ ቪ ኤድስ ቀንን አክብሯል። የኢንዱስትሪ ፓርኩ ሥራ አሥኪያጅ የሽጥላ ሙሉጌታ የግንዛቤ ፈጠራ ሥራዉ በሚጠበቀዉ ደረጃ ባለመኾኑ በኢንዱስትሪ ፓርኮችና በግዙፍ የግንባታ ቦታዎች ላይ የቫይረሱ ስርጭት እንዲጨምር ምክንያት መኾኑን ተናግረዋል።

የወጣቶችን እና የአምራች ወገኖችን ሕይወት የሚቀጥፈዉን ቫይረስ ለመከላከል ቀጣይነት ያለዉ ሥራ መሥራት እንደሚያስፈልግም ተናግረዋል። ኢንዱስትሪ ፓርኩ ከተለያዩ አካባቢዎች የመጡ አልሚዎች እና ሠራተኞች የሚገኙበት በመኾኑ እለቱን አስታዉሶ ግንዛቤ የማስጨበጥ ሥራ መሥራትም ያስፈልጋል ነዉ ያሉት።

የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት መረጃ እንደሚያሳየዉ በየዓመቱ ከ7 ሺህ በላይ ሰዎች በአዲስ በኤች አይ ቪ ቫይረስ ይያዛሉ ። በእለቱም “የሴት ጥቃት የእኔም ጥቃት ነዉ!” በሚል መሪ ሃሳብ የነጭ ሪቫን ቀንም ተከብሯል።

ዘጋቢ:_ ብርቱካን ማሞ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየጎንደር ኮሪደር ልማት የከተማዋን ታላቅነት የመለሰ መኾኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ገለጹ።
Next articleሕዝብ የሚያለያይ ሳይኾን ሕዝብን የሚያገናኝ ትርክትን ማስቀጠል እንደሚገባ የክልል ምክር ቤት አፈ ጉባኤዎች አሳሰቡ።