ክልላዊ የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን የማጠቃለያ ዝግጅት ላይ ለመታደም የተለያዩ የፌዴራል እና የክልል መሪዎች ጎንደር ከተማ ገቡ።

49

ጎንደር: ኅዳር 25/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ክልላዊ 19ኛው የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን የማጠቃለያ ዝግጅት በጎንደር ከተማ ይከበራል። በዓሉን ለማክበር የፌዴራል እና የክልል መሪዎች ጎንደር ከተማ ገብተዋል።

የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፣ የአማራ ክልል ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አብዱ ሁሴን (ዶ.ር) ጨምሮ የተለያዩ የፌዴራል እና የክልል መሪዎች በክልል ደረጃ ለሚከበረው ማጠቃለያ በዓል ጎንደር ለመታደም ከተማ ገብተዋል።

ጎንደር ከተማ ሲገቡ የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ምክር ቤት አፈ ጉባኤ እናትነሽ ዋለ፣ የጎንደር ከተማ አሥተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ቻላቸው ዳኘው፣ የጎንደር ከተማ ምክትል ከንቲባ ደብሬ የኋላ፣ የማዕከላዊ ጎንደር ዞን አሥተዳዳሪ አወቀ አስፈሪ እና ሌሎች የሥራ ኀላፊዎች እንዲሁም ከከተማዋ የተወጣጡ የሃይማኖት አባቶች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

በያየህ ፈንቴ

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article19ኛው የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በአማራ ክልል የማጠቃለያ ዝግጅት በጎንደር ከተማ ይከበራል።
Next articleአሥተዳደራዊ ቅሬታዎችን በአደባባይ ለመፍታት የሚደረገው ጥረት ወደ ሌሎች ከተሞች መስፍት አለበት።