ከ900 በላይ ወጣቶች የሰላም ዘብ ለመኾን ሠልጥነው ወደ ሥራ ገቡ።

51
ጎንደር: ኅዳር 22/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በጎንደር ከተማ አሥተዳደር አሁን ያለውን የሠላም ኹኔታ የበለጠ አስተማማኝ ለማድረግ ከሁሉም ክፍለ ከተሞች የተውጣጡ ከዘጠኝ መቶ በላይ ወጣቶች ተመርቀው ወደ ሥራ ገብተዋል።
ወጣቶቹ ለአስራ አምስት ቀናት የሙያ እና የጽንሰ ሀሣብ ሥልጠና የወሰዱ ናቸው። በጎንደር ከተማ የሚስተዋሉ የዝርፊያ፣ የግድያ እና የእገታ ወንጀሎችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በየቀበሌዎቹ ለመሠማራት ዝግጁ መኾናቸውን ወጣቶቹ ተናገረዋል።
ወጣቶቹ በከተማዋ ያሉ የልማት ሥራዎችን ተዘዋውረው በመጎብኘት ላይ ናቸው። ከጉብኝት በኋላ የሥልጠና ማጠቃለያ መድረክ ይካሄዳል ተብሎ ይጠበቃል።
የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!
Previous articleሳምንቱ በታሪክ
Next articleመገናኛ ብዙኀን ስለ ሥነ-ተዋልዶ ጤና መረጃ ሲያደርሱ ጥንቃቄ እንዲያደረጉ ተጠየቀ።