በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከ561 ቶን በላይ ዓሣ ተመርቷል።

14

ባሕር ዳር: ኅዳር 20/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በዓሣ ምርት የተሠማሩ 22 ማኅበራት ከባለፈው ሐምሌ ወር ጀምሮ 561 ነጥብ 5 ቶን የዓሣ ምርት ለአካባቢው እና ማዕከላዊ ገበያ አቅርበዋል።

ግድቡ ከኃይል ማመንጨት ባለፈ ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠሩን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ የእንስሳት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ ብርሃኑ ኢተቻ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

በዓሣ ማምረት ለተሠማሩ ማኅበራትም የማምረቻ ቁሳቁሶችን ጨምሮ የገበያ ትስስር መፈጠሩን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየሳይበር ሉዓላዊነት
Next articleየሰሜን ጎጃም ዞን የእርሻ ትራክተሮችን ለተጠቃሚ አርሶ አደሮች አስረከበ።