“የማንለያይ የጤፍ ዘሮች ነን” የአማራ እና የኦሮሚያ ክልል ነዋሪዎች

18

ደብረ ብርሃን: ኅዳር 19/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ለ19ኛ ጊዜ የሚከበረው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ቀን በዓል “ሀገራዊ መግባባት ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ሃሳብ በሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ ወረዳ ተከብሯል።

በዓሉን በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን አንጎለላ ጠራ እና በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ቅምብቢት ወረዳ የሚገኙ ነዋሪዎች በጋራ አክብረውታል።

የበዓሉ ታዳሚዎች ይህንን በዓል ስናከብር ለዘመናት ይዘነው የዘለቅነውን አብሮነት ለማስቀጠል ይረዳናል ብለዋል።

“እኛ ለመለያየት የምንከብድ የጤፍ ዘር ነን” ሲሉ ቁርኝታቸውን የገለጹት ተሳታፊዎቹ ይህንን አንድነታችንን ለበጎ ተግባር እንጠቀምበታለን ብለዋል።

የሰሜን ሸዋ ዞን ሲቪል ሰርቪስ መምሪያ ኀላፊ ሜሮን አበበ መልካም እሴቶቻችንን ለመለዋወጥ እና አንድነታችንን ለማጠንከር ባለመ መልኩ በዓሉን በጋራ አክብረናል ብለዋል።

ዘጋቢ፦ ለዓለም ለይኩን

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!

👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየብልጽግና ፓርቲ አምስተኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር በባሕር ዳር እየተካሄደ ነው።
Next articleበአማራ ክልል ከ1 ሚሊዮን በላይ ለሚኾኑ የወባ በሽታ ታማሚዎች የመድኃኒት አቅርቦት እና ሕክምና ተሰጥቷል፡፡