በባሕር ዳር ከተማ የተገነባው የገበያ ሸድ ለተጠቃሚዎች ተላለፈ፡፡

47

ባሕር ዳር: ኅዳር 19/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር በስላሴ ጉልት ገበያ ያስገነባውን የገበያ ሸድ ለ526 ነጋዴዎች አስረክቧል።

የባሕርዳር ከተማ አሥተዳደር አገልግሎት ጽሕፈት ቤት አሥተባባሪነት በማኅበረሰቡ ተሳትፎ እና በረጅ ድርጅቶች ድጋፍ የተገነቡ የገበያ ሸዶች ለተጠቃሚው መተላለፋቸው ነው የተገለጸው፡፡

የከተማዋን ሰላም ከማስከበር ጎን ለጎን የልማት እና መልካም አሥተዳደር ግንባታ ሥራንም ውጤታማ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ እንደኾነ ነው የተገለጸው፡፡

በስላሴ ገበያ ማዕከል ይሠሩ የነበሩ 108 ሴት ነጋዴዎች በተሠራው የልማት ሥራ ተጠቃሚ መኾናቸውን ከከተማ አሥተዳደሩ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ባሕር ዳር ከተማ በተፈጥሮ የተዋበች፣ ለኑሮ የተመቸች፣ የጎብኚዎች ማዕከል የኾነች ከተማ ናት” ሰማ ጥሩነህ (ዶ.ር)
Next articleየብልጽግና ፓርቲ አምስተኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ክልላዊ የማጠቃለያ መርሐ ግብር በባሕር ዳር እየተካሄደ ነው።