
የኮሪደር ልማት የጣና ዳር ፈርጧ ባሕርዳርን ተጨማሪ ውበት የሚያላብሳት ከመሆኑም በተጨማሪ ለነዋሪዎቿ፣ ቱሪስቶች እና በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ከተማዋ ለሚመጡ እንግዶች የምትመች የሚያደርግ ነው፡፡
ዛሬ በባሕር ዳር ከተማ ተገኝተን የመጀርያው ዙር የኮሪደር ልማት ሥራን ተመልክተናል፡፡
በጥቂት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ የታሰበው የመጀመርያው ዙር የኮሪደር ልማት ቀን ከሌት በትጋት እየተሰራ ይገኛል፡፡
የኮሪደር ልማት ሥራው በተጀመረው ትጋት እና ብርታት ተጠናቆ ሳይክል መጠቀም ባሕላቸው ለሆነው የከተማይቱ ነዋሪዎች ለአገልግሎት ክፍት እንደሚሆን አይተናል፡፡
መንግስት የከተሞች ውበት እና የተጥሮ ሀብት ተጠብቆ እንዲዘምኑና የቱሪስት መስህብነታቸው እንዲጨምር በትኩረት መሥራቱን ይቀጥላል፡፡
