ወጣቶች በሀገራዊ ምክክር ሂደቶች ላይ መሳተፋቸው ለምን አስፈለገ?

33

ባሕር ዳር: ኅዳር 13/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ወጣቶች በሀገራዊ ምክክር ሂደቶች ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ይጠበቃል፡፡

ወጣቶች በሀገራዊ ምክክር ሂደቶች ላይ መሳተፋቸው በዋናነት ከታች የተዘረዘሩትን ዋና ዋና ጉዳዮች ለመመለስ ያግዛል፡፡
👉 ወጣቶች በግጭቶች እና አለመግባባቶች የበለጠ ተጎጅ በመኾናቸው፤
👉 ወጣቶች በኢትዮጵያ የሥነ ሕዝብ ምጣኔ ውስጥ ከአንድ ሦስተኛ በላይ ቁጥር ያላቸው መኾኑ እና ይኽም በጉዳዩ ላይ ዋነኛ ከዋኝ እንዲኾኑ ስለሚያስችላቸው፤
👉 ወጣቶች ሀገር ተረካቢ በመሆናቸው እና ስለነገው የሀገራቸው ጉዳይ ባለቤት በመኾናቸው፤
👉 ወጣቶች ለለውጥ ያላቸው ፍላጎት ከፍተኛ በመኾኑ አዳዲስ አስተሳሰቦችን እና አመለካከቶች በምክክር ሂደቶች ለማስተናገድ ቅርብ መሆናቸው፤
👉 በወጣቶች ጥያቄ የነገ ሀገር ስለምትፀና የሚሉት ናቸው፡፡

ምንጭ፡- የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

የአሚኮ ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇
https://linktr.ee/AmharaMediaCorporation

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየወልድያ ከተማ አሥተዳደር የኮሌራ መከላከያ ክትባት መስጠት ጀመረ።
Next articleየኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር ሃብት በማሰባሰብ በገንዘብ ራሱን ለመቻል የሚያደረገውን ጥረት እንደሚያግዙ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ ተናገሩ።