
ባሕር ዳር: ኅዳር 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የብልፅግና ፓርቲ ከፍተኛ መሪዎች እና የሁሉም ክልልና ከተማ አሥተዳደር የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊዎች ታላቁን የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጎብኝተዋል።
ከፍተኛ መሪዎቹ የግድቡን አጠቃላይ ነባራዊ ሁኔታ እና የተለያዩ ክፍሎቹን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።
የኢዜአ ዘገባ እንደሚያመላክተው የፕሮጀክቱ አሥተባባሪዎችም ሥራው የደረሰበትን ደረጃ ለጎብኝዎቹ አብራርተዋል።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!