የሀገር ውስጥ የግሉ ዘርፍ ምርታማነት ሀገራዊ የኢንዱስትሪ ልማትን ከግብ ለማድረስ እንደሚያስችል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ገለጹ።

54

ባሕር ዳር: ኅዳር 09/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶር) የሀገር ውስጥ የግሉ ዘርፍ ምርታማነት ሀገራዊ የኢንዱስትሪ ልማታችንን ከግብ ለማድረስ እና ኢኮኖሚያችንን ለማጠናከር ወሳኝ ሚና ይጫወታል ብለዋል በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት።

“ዛሬ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄን የሚመሩ ትልልቅ ኢንዱስትሪዎችን ጎብኝቻለሁ። ዕሴት በተጨመረበት ቡና ኤክስፖርት እና ብረታ ብረት ምርት ላይ የተካነው ኤኤምጂ ሆልዲንግስ ኢንዱስትሪ ፓርክ እና በመስተዋት እና በአሉሚኒየም ሥራዎች የሚታወቀው አንድነት መስተዋት ቴክኖሎጂ የግሉ ዘርፍ ለኢንዱስትሪ መስፋፋት እያበረከተ ያለውን አስተዋጽዖ ማሳያ ናቸው” ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየዓሳ ሃብት ልማቱ በመሠረተ ልማት ችግር እየተፈተነ ነው።
Next articleየብሔር በሔረሰቦች ቀንን ምክንያት በማድረግ የንግድ አውደ ርዕይ እና ባዛር በአዲስ አበባ ከተማ ተከፈተ።