የአማራ ክልል የገጠር ዘርፍ የአማራ ክልል የገጠር ዘርፍ ጉድኝት ተቋማት ለሰላሙ ያላቸውን አበርክቶ የሚዳሰስ እና በቀጣይ ጊዜ ተግባራት ላይም አቅጣጫ የሚያስቀምጥ መድረክ እየተካሄደ ነው፡፡

26

ባሕር ዳር: ኅዳር 5/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የአማራ ክልል የገጠር ዘርፍ ጉድኝት ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት አንደኛ ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸማቸውን እየገመገሙ ነው።

በግምገማ መድረኩ ምክትል ርእሰ መሥተዳድር አቤዱ ሁሴን (ዶ.ር)፣ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኀላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ.ር) እና የየተቋማቱ ከፍተኛ መሪዎች እንዲሁም የማኔጅመንት አባላት ተገኝተዋል።

የተቋማቱ ያለፈው ሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም በሚገመገምበት በዚሁ መድረክ ከመደበኛ ሥራ በተጨማሪ ለሰላሙ ያላቸውን አበርክቶ የሚዳሰስ ሲኾን በቀጣይ ጊዜ ተግባራት ላይም አቅጣጫ እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑን በደንብ ከተጠቀምንበት ለአማራ ሕዝብ ስጦታ ነው፡፡
Next article“የምናልመውን ለውጥ ለማምጣት ሁሉም መሪዎች ሥራን በጋራ እና በጠንካራ ክትትል ማከናወን አለባቸው” ርእሰ መሥተዳደር አረጋ ከበደ