ከ472 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ የጫነች የመጀመሪያዋ መርከብ ጅቡቲ ወደብ መድረሷ ተገለጸ፡፡

62

ባሕር ዳር: ጥቅምት 29/2017 ዓ.ም (አሚኮ)በ2017/18 የምርት ዘመን ከውጭ ከሚገዛው 23 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ውስጥ 472 ሺህ 500 ኩንታል ዩሪያ የጫነች የመጀመሪያዋ ኤም ቪ ዓባይ ሁለት የተሰኘች የኢትዮጵያ መርከብ ጅቡቲ ወደብ ደርሳለች።

በቀጣይ ቀናትም የሰው ሠራሽ ማዳበሪያውን ወደ ሀገር ውስጥ የማጓጓዝ ሥራም በፍጥነት እንደሚጀመር ይጠበቃል።

ለ2017/18 የምርት ዘመን ለ23 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪ ግዥ 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ተመድቧል።

እንደ ኢፕድ ዘገባ መንግሥት አዲስ የግዥ መመሪያ በማውጣቱ ባለፈው የምርት ዘመን 21 ቢሊዮን ብር ለማዳን መቻሉን የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን መረጃ ያመለክታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየ5ኛ ትውልድ የመረጃ መረብ!
Next articleየግሪሳ ወፍን ለመከላከል የኬሚካል ርጭት መደረጉን የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ገለጸ።