በርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የተመራ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በሰሜን ሸዋ ዞን በኩታ ገጠም የለማ ሰብልን እየጎበኙ ነው፡፡

75

ደብረ ብርሃን: ጥቅምት 28/2017 ዓ.ም (አሚኮ)በርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የተመራ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች በሰሜን ሸዋ ዞን በሲያደብርና ዋዩ ወረዳ በኩታ ገጠም የለማ ሰብልን እየጎበኙ ነው፡፡

በሰሜን ሸዋ ዞን በሲያደብርና ዋዩ ወረዳ በኩታ ገጠም የለማ ሰብልን ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደን ጨምሮ የአማራ ክልል ዋና አፈጉባኤ ፋንቱ ተስፋዬ፣ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ እና የግብርና ቢሮ ኀላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ.ር)፣ በምክትል ርእሰ መሥተዳድር ማዕረግ የከተማ ልማት ዘርፍ አስተባባሪ እና የከተማ እና መሠረተ ልማት ቢሮ ኀላፊ አሕመዲን መሐመድ (ዶ.ር) እና ሌሎች የክልል እና የዞኑ ከፍተኛ የሥራ ኀላፊዎች እየጎበኙ ነው፡፡

ጉብኝቱ በሲያደብርና ዋዩ ወረዳ ሮሜ ቀበሌ ነው እየተካሄደ የሚገኘው።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ብልፅግና ፓርቲ እጅግ በበዙ ውስብስብና እልህ አስጨራሽ ፈተናዎች የታጀበ የትግል፣ የተግዳሮትና የለውጥ ዓመታትን ያሳለፈ ፓርቲ ነው” አቶ ይርጋ ሲሳይ
Next articleበዓለም ዘላቂ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ግብርናን መገንባት እንደሚገባ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ.ር) ተናገሩ።