
ደብረ ታቦር: ጥቅምት 25/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በደቡብ ጎንደር ዞን የነፋስ መውጫ ከተማ እና የላይ ጋይንት ወረዳ አስተዳደሮች በቅንጅት ባዘጋጁት “ሠላም ለሁሉም ሁሉም ለሠላም” በሚል መራ ሀሳብ የተዘጋጀ ሀገራዊ፣ ወቅታዊ እና ሕዝባዊ የሠላም ኮንፈረንስ መካሄድ ጀምሯል።
የኃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ምሁራን፣ ሴቶች ወጣቶች እና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች የመድረኩ ተሳታፊዎች ናቸው።
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!