የሰላም ሚኒስቴር እና የመሀመድ ቢን ዛይድ ዩኒቨርሲቲ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት አደረጉ።

36

ባሕር ዳር: ጥቅምት 25/2017 ዓ.ም (አሚኮ) ኢትዮጵያ ያዘጋጀችውን ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፍረንስ ዛሬ በኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የሰላም ሚኒስትሩ ብናልፍ አንዱዓለም እና የመሀመድ ቢን ዛይድ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ከሊፋ ሙባረክ (ዶ.ር) ተከፍቷል።

በዚሁ መድርክ ላይ የኢፌዲሪ የሰላም ሚኒስቴር እና የመሀመድ ቢን ዛይድ ዩኒቨርሲቲ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን ስምምነት ፈጽመዋል።

ስምምነቱን የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ድኤታ ከይረዲን ተዘራ (ዶ.ር) እና የመሀመድ ቢን ዛይድ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ከሊፋ ሙባረክ (ዶ.ር) ፈርመውታል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የሠራናቸው ሥራዎች ተጽዕኗቸው ድንበር ተሻጋሪ ነው” ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ
Next articleበፀጥታ ችግር ምክንያት የተቋረጡ የልማት ሥራዎች ወደ ሥራ እንዲገቡ ወጣቱ ለሰላም እንዲሠራ የደብረ ማርቆስ ከተማ አሥተዳደር አሳሰበ፡፡