ኢትዮጵያ ያዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ተከፈተ።

16

ባሕር ዳር: ጥቅምት 25/2017 ዓ.ም (አሚኮ)ኢትዮጵያ ያዘጋጀችው ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ ዛሬ በአዲስ አበባ ተከፍቷል።

ይህንን ዓለም አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ኮንፈረንስ የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ፣ የሰላም ሚኒስትሩ ብናልፍ አንዱዓለም እና የመሐመድ ቢን ዛይድ ዩኒቨርሲቲ ቻንስለር ዶክተር ከሊፋ ሙባረክ ከፍተውታል።

በኮንፈረንሱ ላይ ከ16 ሀገራት የተውጣጡ የሃይማኖት አባቶችና የተቋማት መሪዎች እየተሳተፉ ነው።

ኢፕድ እንደዘገበው ኮንፈረንሱ በልዩ ልዩ መርሐ ግብሮች እስከ ነገ እንድሚቀጥል ታውቋል።

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ዘመናዊ የእርሻ ትራክተሮች ገዝተን ለአርሶ አደሮች አስረክበናል” የሰሜን ጎጃም ዞን ግብርና መምሪያ ምክትል ኀላፊ መልካሙ አለኸኝ
Next articleየመርጦለማርያም ከተማ እና የአካባቢው ማኅበረሰብ በወቅታዊ የሰላም ጉዳዮች ላይ እየመከሩ ነው፡፡