“የዲጂታላይዜሽን የሪፎርም ሥራዎች በምህንድስናው ዘርፍ ኮርፖሬሽኑን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ናቸው” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

50

ባሕር ዳር: ጥቅምት 10/2017 ዓ.ም (አሚኮ)ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በምህንድስናው ዘርፍ ወጤታማ ስኬቶችን ለማስመዝገብ የዲጂታላይዜሽን ትግበራ ትልቅ ፋይዳ አለው ብለዋል፡፡

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በባሕር ዳር ከተማ የሚገኘውን የልህቀት ዲዛይንና ቁጥጥር ኮርፖሬሽን የሪፎርም ሥራዎችን መጎብኘታቸውንም ነው የገለጹት፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ የተመለከትናቸው ምቹ የሥራ ከባቢ ግንባታ እና የዲጂታላይዜሽን የሪፎርም ሥራዎች በምህንድስናው ዘርፍ ኮርፖሬሽኑን ወደ ተሻለ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ናቸው ብለዋል፡፡
ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleመምህር የሰላም ሚናው የጎላ በመኾኑ ይህን ታሳቢ አድርጎ መሥራት እንደሚገባ የሰሜን ጎንደር ዞን ዋና አሥተዳዳሪ ዲያቆን ሸጋው ውቤ ገለጹ፡፡
Next articleቤዛዊት ቤተ-መንግሥት ለቱሪስቶች ክፍት እንዲደረግ ተጠየቀ፡፡