ሴቶች በዲጂታል ዘርፉ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዲኾኑ መደገፍ እንደሚገባ በለጠ ሞላ (ዶ.ር) አሳሰቡ።

51

አዲስ አበባ:ጥቅምት 08/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበረ ያዘጋጁት የሴት ስታርታፖች ውድድር የመዝጊያ ፕሮግራም ተካሂዷል። ከመላው የሀገሪቱ ክፍሎች የተውጣጡ 37 ሴት ስታርታፖች የተሳተፉበት ውድድር ዛሬ ሲጠናቀቅ አሸናፊ ለኾኑት 10 ተወዳዳሪዎች ለእያንዳንዳቸው የ100 ሺህ ብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ.ር) ሴቶች የሚሳተፉበት ኢኮኖሚ የመለወጥ እድሉ ከፍተኛ መኾኑን ገልጸዋል። በአይሲቲ/ICT/ ኢኖቬሽን ዘርፍ የሕዝቡን ሕይወት ለመቀየር ወጣት እና ሴቶችን ማብቃት ላይ መሥራት አለብን ብለዋል። በዘርፉ ምቹ ኹኔታዎችን ለመፍጠር ደግሞ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ሁሉ ፖሊሲ በመቅረጽ እገዛ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል።

ሴት ስታርታፖቹ በአይቲ ፓርክ ኢኖቢዝ – ኬ ኢትዮጵያ ማዕከል ውስጥ ላለፉት 10 ቀናት የተለያዩ የክህሎትና የቢዝነስ ሥልጠናዎችን ሲወስዱ መቆየታቸውም ተገልጿል።

ዘጋቢ:- ቤተልሄም ሰለሞን

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleኅብረተሰቡ ለወባ በሽታ ስርጭት ትኩረት ባለመስጠቱ የከፋ ጉዳት እየደረሰ መኾኑን የምዕራብ ጎንደር ዞን ጤና መምሪያ አስታወቀ፡፡
Next articleየወባ በሽታ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ በመምጣቱ ጥንቃቄ እንዲደረግ የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር አሳሰበ፡፡