በባሕርዳር በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 3 ሺህ ሊትር ነዳጅ ተያዘ።

44

ባሕር ዳር: ጥቅምት 06/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በባሕርዳር ዳር ከተማ ግሽ አባይ ክፍለ ከተማ በሕገ-ወጥ መንገድ ሲንቀሳቀስ የነበረ 3 ሺህ ሊትር ነዳጅ ተያዘ፡፡

ነዳጁ በሕገ-ወጥ መንገድ ከማደያዎች በሌሊት ተቀድቶ ሲወጣ በተደረገ ክትትል ከነተጠርጣሪዎቹ እጅ ከፍንጅ መያዙን የክፍለ ከተማው ሰላምና ጸጥታ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።

10 በርሚል እና ከ50 በላይ ባለሁለት ሊትር ቤንዚን በክትትል ከተጠርጣሪዎቹ እጅ እንደተገኘም የከተማዋ ኮሙኒኬሽን መረጃ አመልክቷል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous article“ብዙዎችን የለወጠው ቅመማ ቅመም”
Next article“ያጋጠሙንን ተግዳሮቶች ፈጥነን በመሻገር ሁለንተናዊ ልማታችንን ማፋጠን ላይ በትኩረት መረባረብ ይገባናል” ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ