ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከአውሮፓ ኅብረት ዓለም አቀፍ ትብብር ኮሚሽነር ጋር ተወያዩ።

38

ባሕር ዳር: ጥቅምት 05/2017 ዓ.ም (አሚኮ)የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ ከአውሮፓ ኅብረት ዓለም አቀፍ የትብብር ኮሚሽነር ጁታ ኡርፒላይነን ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም የሁለትዮሽ ሀገራዊ፣ ቀጣናዊ እና ባለብዙ ወገን ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ፕሬዚዳንት ታዬ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት ገልጸዋል፡፡

የአውሮፓ ኅብረትን አጋርነት በይበልጥ ማሳደግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይም የሚከናወኑ ሥራዎች ተጠናክረው በሚቀጥሉበት ሁኔታ ላይ መስማማታቸው ተገልጿል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleየአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ከቀረቡለት ቅሬታዎች ውስጥ 88 በመቶ ምላሽ መስጠቱን አስታወቀ።
Next article“ካለው ሰፊ ችግር አንጻር እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች በቂ አይደሉም” ዋና ዳይሬክተር በላይ በዛብህ