“ብዙ ሁነን እንደ አንድ በመቆም ለኢትዮጵያ ከፍታ የምንነሳበት ጊዜ ነው” ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀሥላሴ

69

አዲስ አበባ: ጥቅምት 04/2017 ዓ.ም (አሚኮ)“ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችን እና ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ መልዕክት የሰንደቅ ዓላማ ቀን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተከብሯል።

በመርሐ ግብሩ የተገኙት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀሥላሴ የሰንደቅ ዓላማ ቀን ትርጉም ባለው መንገድ ለሀገራዊ አንድነት በመትጋት ሊከበር ይገባል ብለዋል።

“ሰንደቃችን የመሥዋዕትነት፣ የነፃነት፣ የሉዓላዊነታችን መገለጫ እና አርማችን ነው” ብለዋል ፕሬዚዳንቱ።

ጊዜው ከመቸውም በላይ አንድነታችንን የምናጸናበት እና ኢትዮጵያን መካከለኛ ኢኮኖሚ ካላቸው ሀገራት ጋር እንድትሰለፍ የምናደርግበት ነው ብለዋል።

ዘጋቢ፡- ራሄል ደምሰው

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበኮንትሮባንድ ንግድ ሀገር ልታጣ የነበረውን ከ50 ቢሊዮን ብር በላይ ማዳን መቻሉን የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ።
Next article“በልጆችሽ የተከበርሽ፤ ጠላቶችሽ የማይደፍሩሽ”