የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዛሬ ምሽት ከጊኒ አቻው ጋር ይጫወታል።

54

ባሕር ዳር: ጥቅምት 02/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከጊኒ አቻው ጋር ምሽት 1፡00 ሰዓት ላይ በአቢጃን ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

ለዚህም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አስቀድሞ ወደ ኮትዲቯር አቢጃን የተጓዘ ሲሆን ለዛሬው ጨዋታ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱ ተጠቁሟል፡፡

በጨዋታው አማካዩ ቢኒያም በላይ በጉዳት ከመጨረሻዎቹ ልምምድ ውጭ መሆኑ ሲገለጽ÷ሌሎች ተጫዋቾች በመልካም ጤንነት ላይ እንደሚገኙና ለጨዋታው ዝግጁ መሆናቸውን ፌደሬሽኑ አስታውቋል፡፡

ለኅብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!

Previous articleበባሕር ዳር የተከናወኑ የልማት ሥራዎች ለቱሪስቶች ምቹ ከተሞች ግንባታ ማረጋገጫ መኾናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመሥገን ጥሩነህ ገለጹ።
Next article“ዋልያዎቹ ዛሬ ከጊኒ ጋር ለሚያደርጉት ጨዋታ የመጨረሻ ልምምዳቸውን በሊሴ ሞደርን ዲ’ኮኮዲ ሜዳ አከናውነዋል” የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን